መቅዳላ አምባ ዩኒቨርሲቲ በሶስት የትምህርት ክፍሎች የማስተርስ ፕሮግራም ለመክፈት በውጭ ገምጋሚወች አስገመገመ፡፡

Latest News

ግምገማውን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶክተር ካሳ ሻወል እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲው ባለፉት አራት አመታት በ22 የትምህርት ክፍሎች በመጀመሪያ ድግሪ ሲያስተምር የቆየ መሆኑን አስታውሰው በተጨማሪም ፕሮግሞቹን ለማሳደግ  6 የመጀመሪያ ግድሪና 4 የሁለተኛ ድግሪ ለመክፈት አቅዶ ሲሰራ ቆይቷል፡፡አሁንም የዚህ አካል የሆነው በዩኒቨርሲቲው ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ  በሶስት የትምህርት ክፍሎች ማለትም MSC. In Development Economics, MA in Teaching English as a foreign Language/TEFL/, MSC in Animal Production የማስተርስ ፕሮግራም ለመክፈት ጥራቱን የጠበቀ ካሪኩለም እንድዘጋጅ  በውጭ ገምጋሚወች  ማስገምገሙ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

እነዚህ ፕሮግራሞች በትምህርት ክፍሎች፣በኮሌጆችና በዩኒቨርሲቲው ሴኔት  በየደረጃው ውይይት ተደርጎባቸው የትምህርት ተደራሽነትንና ለአካባቢው ማህበረሰብ ከሚኖረው ፋይዳ አኳያ እንድከፈቱ ውሳኔ የተደረሰባቸው ሲሆኑ ትምህርቱንም ለማስጀመር በቂ ዝግጅት ስለተደረገ የተማሪ ጥሪ በማድረግ  በቱሉ አውልያ ካምፓስ MSC. in Animal Production እና በመካነሰላም ካምፓስ MSC. In Developmente Economics  and MA. in Teaching English as a foreign Language/TEFL/  በቅርቡ ማስተማር እንደሚጀምርም አክለው ገልፀዋል፡፡

                                                                                         መስከረም 27/2014 ዓም

Leave a Reply

Your email address will not be published.